Friday, June 21, 2013

ሁለት የመከራና የድል ዓመታት (ስለሺ ሐጎስ)



ጸሀዩ(ጠራራው) መንግስታችን ማብረጃውን ይላክለትና ይኸው፡-

ሀገር አልባ ካረገኝ ሀያ ሁለት ዓመቱ
ወደብ አልባ ካረገኝ ሀያ  ዓመቱ
ፕሬስ አልባ ካረገኝ ሰባት ዓመቱ
ሚስት አልባ ካረገኝ ደግሞ ዛሬ ሁለት ዓመት ሞላው፡፡

ግን አለሁ፤ ያውም በተስፋ፤ ከማለዳ ጸሀይ እጅጉን በፈካ ተስፋ እየኖርኩ ነው፡፡

አንድ ቀን ባለ ሀገር እሆናለሁ እያልኩ ስደትን እርም ብያለሁ፤
አንድ ቀን ኤርትራ ወደ እናት ሀገሯ መመለሷን እያለምኩ የወደብ አልባነት ቁዘማዬን ትቼዋለሁ፤
አንድ ቀን ሀገሬ የነጻነት አምባ እንደምትሆን በፍጹም ልቤ በማመን ልሳናቸው ስለተዘጉ ሚዲያዎቻችን መብሰልሰሌን አቁሚያለሁ፤
አንድ ቀን ርዕዮትን እውነት ነጻ እንደምታወጣት ስለማውቅ ከብቸኝነቴ ጋር እንዲህ እዘምራለሁ፡-

Dear my love,
Our vision prevails over their fear…
Our passion prevails over their power…
Our love prevails over their hate…
Celebrate our vision for freedom, passion for justice, love for humanity and፡
I do celebrate your vision for freedom, passion for justice and love for humanity.
Dear Reeyot, …. I love you!

No comments:

Post a Comment