Main page

Saturday, June 22, 2013

የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን አስቸኳይ ስብሰባ ጠራ

የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን እና የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን
የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን እና የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን
ከኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ጋር በተያያዘ በቅርቡ የተፈጠረውን ቀውስ ምክንያት በማድረግ የሀገሪቷ እግርኳስ ፌዴሬሽን ጉዳዩ የሚመለከታቸው አካሎች ያካተተ አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ የፊታችን ሰኞ (ሰኔ 17, 2005) ቀን በጊዮን ሆቴል ጠራ።
በአለፈው እሁድ አዲስ አበባ ላይ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን የደቡብ አፍሪካ አቻውን 2 ለ 1 በሆነ ውጤት በማሸነፍ በብራዚል አስተናጋጅነት በቀጣዩ አመት በሚካሄደው የአለም ዋንጫ ማጣሪያ የጥሎ ማለፍ ጨዋታ በ13 ነጥቦች ማለፉን ቢያረጋግጥም፣ ከጨዋታው ጥቂት ሰአታት ቆይታ በኋላ የአለም አቀፉ እግርኳስ ፌዴሬሽኖች ማህበር ፊፋ ኢትዮጵያ ከ ቦትስዋና ጋር ከሁለት ሳምንት በፊት ስትጫወት በሁለት ቢጫ ቅጣት መጫወት ያልነበረበት ተጨዋች አሰልፋለች በሚል ምርመራ በመክፈቱ እና የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽንም ጥፋቱን በማመኑ ኢትዮጵያ ቦትስዋናን 2 ለ 1 በማሸነፍ ያገኘችው ሶስት ነጥብ ቅነሳ እና የ 6 ሺህ የስዊዝ ፍራንክ ቅጣትን ለመጋፈጥ ተገዳለች።
የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን ጉዳዩን አስመልክቶ በአለፈው ማክሰኞ ረፋድ ላይ በጠራው ጋዜጣዊ መግለጫ ለክስተቱ ጥፋተኛ ናቸው ያላቸውን ግለሰቦች ስም ዝርዝር ከማቅረቡ በተጨማሪ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴው በጥፋተኞቹ ላይ በቅርቡ ተገቢውን ቅጣት በመውሰድ የቅጣት ውሳኔውን ለህዝብ ይፋ እንደሚያደርግ አስታውቆ ነበር።
የፊታችን ሰኞ የሚካሄደው አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ የተጠራው “የፌዴሬሽኑ የስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ከስልጣን ሊለቅ ስለሆነ ነው” የሚለውን አስተያየት የፌዴሬሽኑ ፕሬዝዳንት አቶ ሳህሉ ገብረወልድ ውድቅ ቢያደርጉትም የውስጥ አዋቂ ምንጮች እንደሚገልጹት ግን ሁሉም የስራ  አስፈጻሚ ኮሚቴ አባል ባይሆንም የሚለቁ ግለሰቦች እንደሚኖሩ ይናገራሉ።
የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን አስቸኳይ ስብሰባ የጠራበት ደብዳቤ
የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን አስቸኳይ ስብሰባ የጠራበት ደብዳቤ
የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን የፊታችን ጳጉሜ ወር ከመሀከለኛው አፍሪካ ሪፐብሊክ ጋር በጥሎ ማለፍ መልክ ወደሚካሄደው የአለም ዋንጫ ማጣሪያ ለማለፍ የምድቡ የመጨረሻውን እና ወሳኙን ጨዋታ ያደርጋል።

No comments:

Post a Comment